Abebech Gobena Charity
መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
________በአበበች ጎበና ህይወት ታሪክ ለይ የተመሰረተ ፊልም ምርቃት እና የገቢ መሰባሰቢያ ኘሮግራም በአድዋ መታሰቢያ አደራሽ ተካሄደ።
በምርቃቱ ስነስርዓት ላይ ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ መስሪያ ቤቶች፣ የፊልም በለሙያዎች፣የአበበች ጎበና ቻሪቲ ጠቅላላ ጉባኤና ቦርድ አባላት እንዲሁም የድርጅቱ ሰራተኞች ተሳትፎበታል።
የፊልሙ አዘጋጅ ጠበቃና ጋዜጠኛ ትሩፋት በላይነህ እንዳሉት በእለቱ የተሰበሰበው ገንዘብ ለአበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ጤና ተቋም ማስፋፊያ የሚውል መሆኑን ጠቅሰው በክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ህይወት ላይ ተመስርቶ የተሰራው ፊልም የእሳቸውን ደግነትና ያለፉበትን ውጣ ውረድ ትዉልድን የሚያስተምርም ነው በለዋል።
በመርሃግብሩ የተለያዩ ድርጅቶች አና ግለሰቦች የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ስሆን በቀጣይነትም ከድርጅቱ ጋር በትብብር ለመስራት ቃል ገብተዋል።